ከልቤ ማህደር
የወደፊት ሂወቴን የኑሮዬን ጎዳና
ብሩህ ላደርግ ስፍጨረጨር ላጎናፅፈው ዋስትና
ከላይ እታች ሥሯሯጥ ሌተ-ቀን ስታትር
የማይሆን ነገር ስሰራ በቁርና በቀትር
ተስፋን በውስጤ አፅድቄ እንጀራዬን ልጋግር
ሕልው መሆኔ ተሽሎኝ መጪው ጊዜዬን ላሳምር ...
አጋሮቼን ሳይ መሰሎቼን ሲለፉ ሲደክሙ ሲጥሩ
ጥቂቶችም ሲያቅታቸው መስሎ መኖር ማደሩ
ልቤ በሃዘን ፍላፃ በፍርሃት ቀስት ሲወጋ
አእምሮዬ ያለእረፍት ሲውል ሲያመሽ ሲያነጋ
የክስተቶችን ምክንያት ምርምርና ፍለጋ...
ያለሜን ጉድፍ ሰንክሳር ምንነትና ማንነት
የሁልቆ መሳፍርት ሁነት እንዴትና ወዴትነት
ማወቅ እየተሳነኝ ስተክዝና ሳቀርቅር
እንባዬም ወደ ውጭ ትቶ ወደ ውስጤ ውስጥ ሲንቆረቆር
ቆይ እስቲ...ደግሞ...በሚል ችካል ወኔዬን ስገነባ
በሕሊናዬ ስቀርፅ ተስፋን በልቤ ሳስገባ ...
ሂወቴ የነበር ቢሆንም ሕልውናዬን ሳልጠላ
ያየሁ ለት ግን ወገን በበረሃ አንገቱ ሲቀላ
የከንቱ ከንቱ እንዳለው ያ ሰው ከኖረባት በሁዋላ
እኔም ምድርን ታዘብኩዋት...ለካ እንዲህ ነች ሌላ...
ልቤ ፈራና ተባ ስሜቴን ማወቅ ተሳነኝ
ስለጠፉ እስትንፋሳት ማሰብ ዳገተኝ መሰለኝ
ይልቅ ራሴን አየሁት እንደ ውጭ ሰው ሆኜ
እናም ምንም ነኝ አልኩኝ እንደጉም የማልቅ በንኜ
ኦ! አንት የምድር የሰማይ ኃይል ሁሉን ተቆጣጣሪ
እንግዲህ ወደ አንተ እንጂ ወደሌላ አይደል የኔ ጥሪ
ወጀቡን እንዳረጋኸው በመፅሐፍ እደተፃፈው
በሰው ህሊና ገብተህ ነውጡን ይበቃል!! በለው....
የወደፊት ሂወቴን የኑሮዬን ጎዳና
ብሩህ ላደርግ ስፍጨረጨር ላጎናፅፈው ዋስትና
ከላይ እታች ሥሯሯጥ ሌተ-ቀን ስታትር
የማይሆን ነገር ስሰራ በቁርና በቀትር
ተስፋን በውስጤ አፅድቄ እንጀራዬን ልጋግር
ሕልው መሆኔ ተሽሎኝ መጪው ጊዜዬን ላሳምር ...
አጋሮቼን ሳይ መሰሎቼን ሲለፉ ሲደክሙ ሲጥሩ
ጥቂቶችም ሲያቅታቸው መስሎ መኖር ማደሩ
ልቤ በሃዘን ፍላፃ በፍርሃት ቀስት ሲወጋ
አእምሮዬ ያለእረፍት ሲውል ሲያመሽ ሲያነጋ
የክስተቶችን ምክንያት ምርምርና ፍለጋ...
ያለሜን ጉድፍ ሰንክሳር ምንነትና ማንነት
የሁልቆ መሳፍርት ሁነት እንዴትና ወዴትነት
ማወቅ እየተሳነኝ ስተክዝና ሳቀርቅር
እንባዬም ወደ ውጭ ትቶ ወደ ውስጤ ውስጥ ሲንቆረቆር
ቆይ እስቲ...ደግሞ...በሚል ችካል ወኔዬን ስገነባ
በሕሊናዬ ስቀርፅ ተስፋን በልቤ ሳስገባ ...
ሂወቴ የነበር ቢሆንም ሕልውናዬን ሳልጠላ
ያየሁ ለት ግን ወገን በበረሃ አንገቱ ሲቀላ
የከንቱ ከንቱ እንዳለው ያ ሰው ከኖረባት በሁዋላ
እኔም ምድርን ታዘብኩዋት...ለካ እንዲህ ነች ሌላ...
ልቤ ፈራና ተባ ስሜቴን ማወቅ ተሳነኝ
ስለጠፉ እስትንፋሳት ማሰብ ዳገተኝ መሰለኝ
ይልቅ ራሴን አየሁት እንደ ውጭ ሰው ሆኜ
እናም ምንም ነኝ አልኩኝ እንደጉም የማልቅ በንኜ
ኦ! አንት የምድር የሰማይ ኃይል ሁሉን ተቆጣጣሪ
እንግዲህ ወደ አንተ እንጂ ወደሌላ አይደል የኔ ጥሪ
ወጀቡን እንዳረጋኸው በመፅሐፍ እደተፃፈው
በሰው ህሊና ገብተህ ነውጡን ይበቃል!! በለው....