Thursday, April 16, 2015




ነሐሴ 5 ቀን 1984 

የሁለተኛ መት የህክምና ትምህርት የንደኛውን ሴሚስተር ፈተና ጠናቀቅን:: ነገ ወደ ዲስበባ ለመሄድ ትኬት ቆርጫለሁ:: አንደድሮው አልቸኮልኩም:: በጉዞ በኩል በጣም የተረጋጋሁ ሰው ሆኛለሁ:: ያለፈው ሴሚስተር የጥናት ብዛትና የተደጋጋሚዎቹ ፈተናዎች ክብደት ያስከተለብኝ የመንፈስ መናወጥ ነው መሰለኝ፤ ለእረፍት ወደ ቤተሰብጋ የምሄድ በመሆኔ ምንም የተሰማኝ ነገር የለም:: ገላዬን ከታጠብኩ ከሳምንት በላይ ሆኗልና ሰውነቴ በተለይም እግሬ ይቀ**ል:: የለበስኩት ልብስም ቆሽሿል:: ወቅቱ በጅማ ክረምት የጠነከረበት ነው እየተባለ ይወራል:: እኔና አኔን መሰሎች ግን በትምህርት ባህር ውስጥ ተዘፍቀን ስለበር የክረምቱን ለውጥ ለማገናዘብ አልታደልንም:: ብቻ መሬቱ ከመጨቅየቱ የተነሳ ነጩን አዲዳስ ጫማዬን አስከማጥበው ድረስ ጥቁር ፈር ይመስል ነበር:: ዶርማችን ታጥቦ ስለማያውቅ ውጭዉን መስሏል:: ጫማዎች አዚያና አዚህ ተጥለው ይታያሉ:: ያልተነጠፉ ልጋዎች ቤቱን የእብድ ቤት ስመስለውታል፥፥ በዶርሙ ውስጥ ከተሰጡት ታጥበው ያልደረቁ ልብሶች የሚወጣው ያደረ ሽታ ላለመደው ሰው ፍንጫ ይሰነፍጣል:: እንዲህ ባለ ሁኔታ  የፒሲዋን ንደኛ ሴሚስተር አለቀ......


No comments:

Post a Comment