ነሐሴ 5 ቀን 1984 አም
የሁለተኛ አመት የህክምና ትምህርት የአንደኛውን ሴሚስተር ፈተና አጠናቀቅን:: ነገ ወደ አዲስአበባ ለመሄድ ትኬት ቆርጫለሁ:: አንደድሮው አልቸኮልኩም:: በጉዞ በኩል በጣም የተረጋጋሁ ሰው ሆኛለሁ:: ያለፈው ሴሚስተር የጥናት ብዛትና የተደጋጋሚዎቹ ፈተናዎች ክብደት ያስከተለብኝ የመንፈስ መናወጥ ነው መሰለኝ፤ ለእረፍት ወደ ቤተሰብጋ የምሄድ በመሆኔ ምንም የተሰማኝ ነገር የለም:: ገላዬን ከታጠብኩ ከሳምንት በላይ ሆኗልና ሰውነቴ በተለይም እግሬ ይቀ**ል:: የለበስኩት ልብስም ቆሽሿል:: ወቅቱ በጅማ ክረምት የጠነከረበት ነው እየተባለ ይወራል:: እኔና አኔን መሰሎች ግን በትምህርት ባህር ውስጥ ተዘፍቀን ስለበር የክረምቱን ለውጥ ለማገናዘብ አልታደልንም:: ብቻ መሬቱ ከመጨቅየቱ የተነሳ ነጩን አዲዳስ ጫማዬን አስከማጥበው ድረስ ጥቁር አፈር ይመስል ነበር:: ዶርማችን ታጥቦ ስለማያውቅ ውጭዉን መስሏል:: ጫማዎች አዚያና አዚህ ተጥለው ይታያሉ:: ያልተነጠፉ አልጋዎች ቤቱን የእብድ ቤት አስመስለውታል፥፥ በዶርሙ ውስጥ ከተሰጡት ታጥበው ያልደረቁ ልብሶች የሚወጣው ያደረ ሽታ ላለመደው ሰው አፍንጫ ይሰነፍጣል:: እንዲህ ባለ ሁኔታ የፒሲዋን አንደኛ ሴሚስተር አለቀ......
No comments:
Post a Comment