ለብላቴ ሰማይ የስራውን ይስጠው
ሚያዚያ ፩ ፩፱፰፫ አ.ም.
ሚያዚያ ፩ ፩፱፰፫ አ.ም.
ምናልባት የምተርፍና የማልሞት ከሆነ የዛሬዋን ቀን መቼም አልረሳትም:: የጠዋቱን ትምህርትና የሰልፍ ስነስርዓት በደንቡ መስረት ስናካሂድ ከሰዓት በሁዋላ ምን እንደሚፈጠር የጠረጠረ በጭራሽ አልነበረም:: ልክ ከቀኑ ስምንት ሰዓት ከሰላሳ ደቂቃ ለፎሌን በፊሽካ ስንጠራ በደከመና በዛለ ሰውነት ብዙም ደስ ባላለው መንፈስ ከየኬስፓናችን ወጣን:: የዛሬው ከሰዓት ትምህርት አይነት የኢላማ ተኩስ ልምምድ ነበር:: ስለዚህም አየርወለዶቹ ከዚህ በፊት ሂደን ወደማናውቅበት ልቅ ና ሜዳማ የሆነ ስፍራ ወሰዱን:: በዙሪያውም ሆነ በሜዳው ላይ ከአንዲት የዘበኛ ማደሪያ ከምትመስል ማማ በስትቀር ምንም አይነት ነገር የለም:: ለጥ ያለ ሜዳ......... ስንደርስ እኔና ጉዋደኞቼ ተልፈስፍሰን ነበር:: ፀሀዩዋ በጣም ከመፋጀቱዋ የተነሳ እዚህ አካባቢ ወደ ታች ወረድ ብላ የምትኖር ነው የሚመስለው::
የሚገርመው ነገር ይህ ሁኔታ አፍታም ሳይቆይ ልክ የመጀመሪያዎቹ ኢላማ ተለማማጆች ስፍራቸውን እንደያዙ ከሁዋላችን በርቀት ከሚገኙት ተራሮች ላይ የተነሳ ኃይለኛ ንፋስ ሜዳው ላይ የነበረውን ዓቡዋራ እያነሳ ሁላችንንም አለበሰን:: ከዚህ በፊት ህወቴን ሙሉ እንዲህ አይነት ጠንካራ ነፋስ አጋጥሞኝ አያውቅም:: ንፋሱ ብዙም ሳይቆይ ቀጥ-ፀጥ አለ::
በዚያው ቅፅበት ተራሮቹ እጅግ በጣም በጠቆረ ዳመና ከዳር እስከ ዳር ተሸፈኑ:: ያልተጠበቀ ዝናም በፍጥነትና በብዛት ይወርድ ጀመር:: ከማደሪያችን አንድ ወይም ሁለት ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ከመሆናችንም ባሻገር ሜዳው ላይም ሆነ በሜዳውና በ ማደሪያችን መካከል ከዝናብ ለመጠለል የሚሆን ምንም አይነት ነገር አልነበረም:: ዝናቡ ደግሞ ብዙ ብቻ ሳይሆን በጣም ቀዝቃዛ ነው:: ዉሽንፍር ና ነፋስ የቀላቀለም ነው:: በስላች የሚወርደው ይህ ዝናብ እያንዳንዱ ጠብታ ትልልቅ ከመሆኑ የተነሳ ፌቴን ሲገርፈኝ እንደ ብዙ ጥፊዎች ነበር የሚሰማኝ::
ተማሪዎች መሮጥና መራወጥ ጀመሩ:: እኔም እንደዛው ለመሮጥ ሞከርኩ የዝናቡና የንፋሱ ከብደት ይበልጥ የተሰማኝ አሁን ነው:: መሮጥ አልቻልኩም:: ብቻ በርምጃና በሩጫ መሃል ያለ እንቅስቃሴ ማድረጌን ቀጠልኩ .......ማዝገም የሚባለው ይሄ ሳይሆን አይቀርም:: የለበስኩት ቱታ ሰውነቴ ላይ ተጣበቀ:: እያዘገምኩ እያለ ከዝናቡ በሁዋላ እታመም ይሆን ብዬ አሰብኩ:::: ነገ በቃ የሆነ በሽታ ይይዘኛል:: ምንም ጥርጥር የለውም:: በጣም ብዙ እጅግ በጣም ብዙ ካዘገምኩ በሁዋላ ዞር ብዬ ሳይ ከሜዳው መቶ ሜትር የሚሆን ብቻ ነው የራኩት:: እዛው ነኝ ብል ይሻላል:: በዚያ ላይ ደከመኝ ::በሚገርም ሁኔታ አንዲት ሁለት የሚሆኑ ቅርንጫፍ ያላት አጭር ዛፍ አየሁ ና እሱዋው ስር ሂጄ ተጠልልኩ:: አንድ ሌላ ተማሪም አብሮኝ ተጠለለ:: አላውቀውም....
በዚያው ቅፅበት ተራሮቹ እጅግ በጣም በጠቆረ ዳመና ከዳር እስከ ዳር ተሸፈኑ:: ያልተጠበቀ ዝናም በፍጥነትና በብዛት ይወርድ ጀመር:: ከማደሪያችን አንድ ወይም ሁለት ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ከመሆናችንም ባሻገር ሜዳው ላይም ሆነ በሜዳውና በ ማደሪያችን መካከል ከዝናብ ለመጠለል የሚሆን ምንም አይነት ነገር አልነበረም:: ዝናቡ ደግሞ ብዙ ብቻ ሳይሆን በጣም ቀዝቃዛ ነው:: ዉሽንፍር ና ነፋስ የቀላቀለም ነው:: በስላች የሚወርደው ይህ ዝናብ እያንዳንዱ ጠብታ ትልልቅ ከመሆኑ የተነሳ ፌቴን ሲገርፈኝ እንደ ብዙ ጥፊዎች ነበር የሚሰማኝ::
ተማሪዎች መሮጥና መራወጥ ጀመሩ:: እኔም እንደዛው ለመሮጥ ሞከርኩ የዝናቡና የንፋሱ ከብደት ይበልጥ የተሰማኝ አሁን ነው:: መሮጥ አልቻልኩም:: ብቻ በርምጃና በሩጫ መሃል ያለ እንቅስቃሴ ማድረጌን ቀጠልኩ .......ማዝገም የሚባለው ይሄ ሳይሆን አይቀርም:: የለበስኩት ቱታ ሰውነቴ ላይ ተጣበቀ:: እያዘገምኩ እያለ ከዝናቡ በሁዋላ እታመም ይሆን ብዬ አሰብኩ:::: ነገ በቃ የሆነ በሽታ ይይዘኛል:: ምንም ጥርጥር የለውም:: በጣም ብዙ እጅግ በጣም ብዙ ካዘገምኩ በሁዋላ ዞር ብዬ ሳይ ከሜዳው መቶ ሜትር የሚሆን ብቻ ነው የራኩት:: እዛው ነኝ ብል ይሻላል:: በዚያ ላይ ደከመኝ ::በሚገርም ሁኔታ አንዲት ሁለት የሚሆኑ ቅርንጫፍ ያላት አጭር ዛፍ አየሁ ና እሱዋው ስር ሂጄ ተጠልልኩ:: አንድ ሌላ ተማሪም አብሮኝ ተጠለለ:: አላውቀውም....
ዋጋ የለውም ራቁቷን የሆነች ዛፍ ስር እጠለላለሁ ብዬ በማሰብ እንደውም ለዝናቡ ቆምኩለት:: ምኑ ሞኝ ነኝ:: ደግነቱ ሌላም ሞኝ አጠገቤ አለ:: ብቻዬን አይደለም የተሞኘሁት:: ከዝናቡ ተጨማሪ ከሁለቱ ቅርንጫፎች እየወረደ የሚመታኝ ወደል ጠብታ ከዝናብ ባሰ:: እንደገና ማዝገሜን ቀጠልኩ:: የሚገርመው ነገር በዚያ በዶፍ መሃል ውሃ ጠማኝ:: አይደረስ የለም ብዬ ብዬ ማደሪያ ኬስፓኔ ደረስኩ:: ምንም ሌላ ያደረኩት ነገር የለም:: አካሌ ላይ የተጣበቀውን ቱታ እንደምንም አወላልቄ ና ጥዬ አልጋዬ ውስጥ ገብቼ ተከናንብኩ:: ከሞትኩም በዚያው ልሙት...እራቴንም አልበላም.....
No comments:
Post a Comment